Wednesday, June 10, 2015



የመቀሌ ዩንቨርስቲ ተማሪ የሰራተኞች ቀንን ያለቀኑ አከበረ
የሰራተኞች ቀን


በናሆም ታደሰ
እለተ ቅዳሜ ሚያዝያ 24 2007 ዓ.ም  በመቀሌ ዩንቨርስቲ በአዲ ሀቂ ግቢ የላባደሮች ቀን ተከብሮ ውሏል። ከትምህርት ጋር የተጋጨበት የግቢው ተማሪ የበአሉን ቀን ከአርብ ሚያዝያ 23 ወደ ቅዳሜ ሚያዝያ 24 2007 ዓ.ም በመሸጋገሩ እለቱን በሚያስደስት ሁኔታ ሲያከብር ተስተውሏል። 

ምንም እንኳን አብዛኛው የበአሉ ተካፋዮች ተሜቂ ተማሪዎች ቢሆኑም ሌሎCM ችተማሪዎች በመጠኑ ተሳትፈዋል። በተለያዩ የስራ መስክ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን ለማሰብ የስራ አልባሳትን ለብሰው ቁሶችን ይዘው በግቢው እየዞሩ በመጨፈር የበአሉን አላማ ለመቃኘት ሞክረዋል። ለአብነት ያክል የመካኒክ ለብስ፤ የቆራሊዮ እቃ የወታደር ትጥቅ እና የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል። 

በወቅቱ በአሉን ሲያከብሩ ከነበሩ ተማሪዊች መካከል የሂስትሪ ተነራቂ ተማሪ የሆነው ዳዊት ቀለምወርቅ ”በአሉ ደስ ይላል። በተማሪዎች መካከል የስራ ተነሳሽነትን የመፍጠር አቅም አለው። በተለይ እኛ ተመራቂ እንደመሆናችን መጠን ነገ ለምንሰራበት የስራ ዘርፍ ይህ በአል የራሱን ሚና እንደሚጫወት አምናለው” ሲል ሀሳቡን አስቀምጧል

No comments:

Post a Comment