Wednesday, August 26, 2015

ምስለ ማሲንቆ

አወይ ማሲንቆዬ…
በፈረሱ ጭራ ለስልሳ የተቃኘች
ከላይ ስነካካት ከስር ገዝግዝ አለች።
እኔ መቼ ገባኝ
ለካ የሲቃው ባቲ ጣፋጭ የሚሆነው
ከስርም እንደላይ ሲገዘግዙት ነው።
ካንቺ ባቆራኘኝ የሙዚቃ ዘመን
እኔ እያለው በይወት ከሌላ ገዝጋዥ እጅ ወድቀሽ ያየሁሽ ቀን
በመገዝገዣዬ ደካማነት ባምንም
ሙዚቀኛሽ እኔ ራስ ወዳድ አልሆንም።
በስልቱ የተካነ በዜማው ከጠራሽ
የሌላ አዝማሪ ግዝገዛ ከረታሽ
እኔ ራሴ ወስጄ ልስጥሽ ለዛ አዝማሪ
በጣቶቹ ርኪ በግዝገዛው ኑሪ
ሂጂ ማሲንቆዬ ለፈረስሽ ጭራ
የሚመጥን ገዝጋዥ ወዳለበት ስፍራ።
ምክንያቱም ትዝታሽ ጣፋጭ የሚሆነው
አምባሰል አንቺሆዬሽ ግሩም የሚሆነው
ከስርም እንደላይ ሲገዘግዙሽ ነው።


ናሆም ታደሰ

1 comment:

  1. Selam nahom endet neh, ye etv meznagnaw azngn sw dnget nw yagegneuh, web blog endaleh bzu sw ayakm slezh bertabet bzu tseraleh,tru chlota alek,azngn gazetegna, aznagn getami, bcha aznagn ye tibeb sw byehalew kelibe dmo yewnet temechegnaleh!
    Ke temelkachih(Ashu) ke sululta

    ReplyDelete